Amhara RoadTransport and Logistics Bureau

Amhara RoadTransport and Logistics Bureau ፕሮጀክት ላንጨረስ አንጀምርም !!

የአማራ ክልል ከፍተኛ መሪዎች የአዋሽ፣ ኮምቦልቻ፣ ሃራ ገበያን የባቡር ፕሮጀክት ዳግም ሥራ አስጀመሩ።*****392 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የባቡር መንገድ ፕሮጀክቱ 2007 ዓ.ም ተጀምሮ እስከ...
17/05/2026

የአማራ ክልል ከፍተኛ መሪዎች የአዋሽ፣ ኮምቦልቻ፣ ሃራ ገበያን የባቡር ፕሮጀክት ዳግም ሥራ አስጀመሩ።
*****
392 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የባቡር መንገድ ፕሮጀክቱ 2007 ዓ.ም ተጀምሮ እስከ 2012 ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቅ ነበር። ኾኖም በሰሜኑ ጦርነት በደረሰበት ውድመት እና ዘረፋ ምክንያት ለመገባደድ ተቃርቦ የነበረው ፕሮጀክት ተስተጓጉሎ ቆይቷል።

ይህ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለው ፕሮጀክት መጠናቀቅ የንግድ ሥርዓቱን በማሳለጥ፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። የባቡር መስመሩ በኤሌክትሪክ ኀይል የሚሠራ ነው።

የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።

ለቱሪዝም እንቅስቃሴ ከፍተኛ ሚና ያለው የባሕር ዳር - ጢስ ዓባይ የመንገድ ፕሮጀክት አፈፃፀምን ለማሻሻል እየተሠራ ነው። 21 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የሚረዝመውን የባሕር ዳር - ጢስ ዓባይ የአ...
15/05/2026

ለቱሪዝም እንቅስቃሴ ከፍተኛ ሚና ያለው የባሕር ዳር - ጢስ ዓባይ የመንገድ ፕሮጀክት አፈፃፀምን ለማሻሻል እየተሠራ ነው።

21 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የሚረዝመውን የባሕር ዳር - ጢስ ዓባይ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈፃፀምን ለማሻሻል እየተሠራ ይገኛል፡፡

እስካሁን ባለው የመንገዱ ግንባታ የዲዛይንና የቅየሳ ሥራዎች ተጠናቀው 16 ነጥብ 44 ኪሎ ሜትር የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ 5 ነጥብ 02 ኪሎ ሜትር የሰብቤዝ፣ 4 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር የቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም 4 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚሆን የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተከናውኗል።

ግንባታው በሀገር በቀሉ መልኮን ኮንስትራክሽን እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን ጎንድዋና ኢንጅነሪንግ ከዋይ ኤል ኤስ ኢንጅነሪንግ ጋር በጥምረት የማማከር ሥራውን እየሠሩት ይገኛሉ።

ለግንባታው የሚውለው 957 ሚሊዮን 930 ሺህ 208 ነጥብ 44 ብር በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው።

በመንገዱ ክልል ውስጥ የሚገኙ ንብረቶች በወቅቱ አለመነሳት፣ የካሳ ክፍያ መዘግየት ፣የአካባቢው የፀጥታ ችግሮች እና የሥራ ተቋራጩ አፈፃፀም ማነስ በሥራው ላይ ጫና ፈጥሮ ቆይቷል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ችግሮቹን ለመፍታት ከአካባቢው መስተዳደር ጋር በመሆን ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።

ይህ የመንገድ ፕሮጀክት የአካባቢውን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለማጠናከር ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ከመሆኑ ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ከባሕር ዳር ከተማ ጋር በማገናኘት የመጓጓዣ ጊዜንና እንግልትን በመቀነስ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው፡፡

መንገዱ እንደ ጤፍ፣ ሸንኮራ እና ሽንኩርት ያሉ የግብርና ምርቶችን በፍጥነት ለገበያ ለማቅረብ ከማስቻሉም በላይ የጢስ አባይ ፏፏቴን ለጎብኚዎች ይበልጥ ተደራሽ በማድረግ የአካባቢውን የቱሪዝም እንቅስቃሴ እንደሚያሳድግ ይታመናል። መረጃው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ነው።

አሚኮ

ቀበሌዎችን ተጠቃሚ ያደረገው  ብራንቲ ቁጥር 2 ኮንክሬት ድልድይ *****በሰሜን ጎጃም ዞን በደቡብ አቸፈር ወረዳ በታድራ ቀልጣፋ  ቀበሌ አምስት ቀበሌዎችን ተጠቃሚ ያደረገው ብራንቲ  ቁጥር ...
15/05/2026

ቀበሌዎችን ተጠቃሚ ያደረገው ብራንቲ ቁጥር 2 ኮንክሬት ድልድይ
*****
በሰሜን ጎጃም ዞን በደቡብ አቸፈር ወረዳ በታድራ ቀልጣፋ ቀበሌ አምስት ቀበሌዎችን ተጠቃሚ ያደረገው ብራንቲ ቁጥር 2 ድልድይ ኮንክሬት አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡

በ4 ነጥበ 2 ሚሊዮን ብር የተገነባዉ የተጠልጣይ ድልድይ ከለውጡ ማግስት ለሞጃ ህዝብ  የተበረከተ ጸጋ መሆኑን የወረዳዉ መንገድና ትራንስፖርት ጽ/ቤት ገለጸ።በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሞ...
15/05/2026

በ4 ነጥበ 2 ሚሊዮን ብር የተገነባዉ የተጠልጣይ ድልድይ ከለውጡ ማግስት ለሞጃ ህዝብ የተበረከተ ጸጋ መሆኑን የወረዳዉ መንገድና ትራንስፖርት ጽ/ቤት ገለጸ።

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሞጃና ወደራ ወረዳ በአይነቱ ልዩ የሆነና ዘርፈ ብዙ ችግሮችን የፈታዉ የእግረኛ ተጠልጣይ ድልድይ ከለዉጡ ማግስት ለሞጃ ህዝብ የተበረከተ ጸጋ መሆኑን የወረዳዉ መንገድና ትራንስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ሸዋይርጋ ገልፀዋል።

ይህ የእግረኛ ተንጠልጣይ ድልድይ ቀበሌዎችን እና አጎራባች ወረዳዎችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ተንጠልጣይ ድልድዩ በመገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብ በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳዉ የጎላ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን አቶ ሰለሞን ሸዋይርጋ ገልፀዋል።

መረጃው የሞጃና ወደራ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

የትራፊክ ኮምፕሌክስ አሰራር መዘመን ለአሽከርካሪ ተሽከርካሪ አገልግሎት አሰጣጥ መሻሻል ድርሻ የጎላ ነው።****በሰሜን ሽዋ ዞን በደብረ ብርሃን ከተማ የአሽከርካሪ ተሽከርካሪ (አሽ/ተሽ) ሙሉ...
14/05/2026

የትራፊክ ኮምፕሌክስ አሰራር መዘመን ለአሽከርካሪ ተሽከርካሪ አገልግሎት አሰጣጥ መሻሻል ድርሻ የጎላ ነው።
****
በሰሜን ሽዋ ዞን በደብረ ብርሃን ከተማ የአሽከርካሪ ተሽከርካሪ (አሽ/ተሽ) ሙሉ አገልግሎት በአዲስ በተገነባው የደብረ ብርሃን ከተማ የትራፊክ ኮምፕሌክስ ህንጻ ውስጥ እየተሰጠ ይገኛል።

በኮምፕሌክሱ ውስጥ ሙሉ የኔትዎርክና የሲስተም ዝርጋታ በማከናወን ዘመናዊና ምቹ የስራ አካባቢ መፍጠር ተችሏል። ይህም ለተገልጋዩ ማህበረሰብ ፈጣን፣ ቀልጣፋና የተቀናጀ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል።

የትራፊክ ኮምፕሌክሱ አሰራር መዘመን የአገልግሎት ጥራትን ከማሻሻል ባለፈ የስራ ቅልጥፍናን በማሳደግ ተገልጋዮች በአጭር ጊዜ አገልግሎት እንዲያገኙ አድርጓል።

የላሊበላ ከተማን የአስፋልት ንጣፍ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። ****** የአማራ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በላሊበላ ከተማ እየለሙ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የሥራ...
12/05/2026

የላሊበላ ከተማን የአስፋልት ንጣፍ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው።
******
የአማራ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በላሊበላ ከተማ እየለሙ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

የሥራ ኀላፊዎቹ የላሊበላ ከተማን የመንገድ ሥራ እና ሌሎችንም ልማቶች ጎብኝተዋል።

የአማራ ክልል መንገድ ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ቢሮ ኀላፊ ጋሻው አወቀ (ዶ.ር) ከጋሸና-ሰቆጣ-ብልባላ ያለውን የአስፋልት መንገድ ለማጠናቀቅ የክልሉ መንግሥት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ መኾኑን ተናግረዋል።

የላሊበላ ከተማን የአስፋልት ንጣፍ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነውም ብለዋል።

የአካፋይ ግንብ እና የድጋፍ ግንብ ሥራዎች መሠራታቸውን አንስተው ለአስፋልት ንጣፍ ዝግጁ መኾኑን ገልጸዋል። በተወሰኑ ቀናት የአስፋልት ንጣፍ ሥራው እንደሚጀመር ተናግረዋል።

የክልሉ መንግሥት ልዩ ክትትል እና ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። ማኅበረሰቡ ለመንገድ ሥራው እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

የሰሜን ወሎ ዞን አሥተዳዳሪ አራጌ ይመር የአገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፋ እንዲኾን፤ ብልሹ አሠራር እንዲቀረፍ እና የዲጂታል አገልግሎት እንዲሳለጥ መንግሥት የሰጠውን ትኩረት ዞኑ ለመተግበር እየሠራ ነው ብለዋል።

በዞኑ በሁለት ከተሞች የአንድ መሶብ አገልግሎት ለማስጀመር እየተሠራ መኾኑን ጠቁመዋል። ግንባታዎቹ እስከ ሰኔ ወር ድረስ እንደሚጠናቀቁ ነው የተናገሩት።

የላሊበላ ከተማ ነዋሪዎችን የመንገድ እና ሌሎች የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች ለመመለስ በትኩረት እየተሠራ እንደኾነ ነው የገለጹት።

የላሊበላን ከተማ የአስፋልት ንጣፍ ከሦስተኛ ወገን ነጻ በማድረግ በተሎ ለመጨረስ እየተሠራ መኾኑንም አንስተዋል።

ቢሮው በተቋማት ሙያዊ ስነ-ምግባርና የልህቀት ሚና” በሚል ርዕስ ስልጠና ሰጠ።*****የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ቢሮ  በተቋማት ሙያዊ ስነ-ምግባርና ...
11/05/2026

ቢሮው በተቋማት ሙያዊ ስነ-ምግባርና የልህቀት ሚና” በሚል ርዕስ ስልጠና ሰጠ።
*****
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ቢሮ በተቋማት ሙያዊ ስነ-ምግባርና የልህቀት ሚና በሚል ርዕስ ስልጠና ሰጠ።

በመንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ቢሮ በቢሮ ሃላፊ ደረጃ አማካሪ የሆኑት ዶክተር አሰፋ በላይ፣ “መንገድ ከሁሉም በላይ የልማት ዋና ምሰሶ በመሆኑ ህብረተሰባችንን በተገቢው ሁኔታ ለማገልገል ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ተቋማዊና ግለሰባዊ ቅንጅትን ማጠናከር ያስፈልጋል” በማለት መድረኩን ከፍተዋል።

የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነዱን ያቀረቡት ከስነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን አቶ ይደግ ልጃለም ሲሆኑ፣ ሰነዱም የሙያዊ ስነ-ምግባር ምንነት፣ አስፈላጊነት፣ ባህሪያት፣ እሴቶች፣ ፈታኝ ሁኔታዎች፣ በሀገር ደረጃ የሙስና ምክንያቶች፣ እንዲሁም ሙስና በሀገር፣ በተቋምና በግለሰቦች እድገት ላይ የሚያሳድረውን አፅዕኖ የሚያብራራ እና አወያይ ሀሳቦችን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።

ከተሳታፊዎችም አንዳንዶቹ እንደገለጹት፣ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ከሚያበረታቱ ጉዳዮች መካከል መረጃዎችን በአግባቡ አለመያዝ፣ ሙሰኛ ባለሙያዎች መሰማራታቸው፣ የባለሙያዎች ክፍያ ዝቅተኛ መሆን፣ ህጎች በተገቢው ሁኔታ ተግባራዊ አለመሆናቸው እና መሰል ጉዳዮች ተጠቅሰዋል።

በቀጣይም ብልሹ አሰራርን በመታገል የተጣለብንን የህዝብ አደራ ለመወጣት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማድረግ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።

በማጠቃለያውም በአብክመ ስነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ማሩ ቸኮል እንደገለጹት፣ “አገራችን በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ እንድትቆይ ከሚያደርጓት ዋና ምክንያቶች አንዱ ሙስናና ብልሹ አሰራር ነው።

ስለሆነም ሁሉም ሰው ብልሹ አሰራርን በማስወገድ፣ በቅንነትና በሀቅ በመስራት የተጣለበትን የህዝብ ኃላፊነት በመወጣት አገራችንን ከችግር ለመታደግ የበኩላችንን ሚና ልንወጣ ይገባል” በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በስልጠናው ላይ የተሳተፉ አጋር አካላት መካከል የስነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን፣ አካባቢ ጥበቃ ቢሮ፣ ገንዘብ ቢሮ፣ ፍትህ ቢሮ፣ ዋና ኦዲት ቢሮ እና ሌሎችም ተቋማት ተገኝተዋል።

የደቡብ ጎንደር ዞን ከፍተኛ አመራሮች በፎገራ ወረዳ እየተሰራ ያለውን  ቲኋ አስፓልት _ድባ_ሴፋጥራ _ርብ ገብርኤል መንገድ ሥራን ጉብኝት አካሂደዋል ።******በደቡብ ጎንደር ዞን በፎገራ ወ...
06/05/2026

የደቡብ ጎንደር ዞን ከፍተኛ አመራሮች በፎገራ ወረዳ እየተሰራ ያለውን ቲኋ አስፓልት _ድባ_ሴፋጥራ _ርብ ገብርኤል መንገድ ሥራን ጉብኝት አካሂደዋል ።
******
በደቡብ ጎንደር ዞን በፎገራ ወረዳ ቲኋ አስፓልት ድባ_ሴፋጥራ _ርብ ገብርኤል ቀበሌ እየተሰራ የሚገኘውን መንገድ ግንባታ የዞን ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ጉብኝት አካሂደዋል።

የፎገራ ወረዳ መንገድ ትራንስፖርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ይትባረክ ፈጠነ በሰጡት አስተያየት ይህ የአዲስ መንገድ ግንባታ መነሻው ድባ -ሲፋጥራ -ር/ገብርኤል የመንገድ ስራ ፕሮጀክት 16 ኪ .ሜ የሚያካልል ሲሆን የገንዘብ ምንጩም የክልሉ መንገድ ትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ቢሮ ከአለም ባንክ ጋር በጋራ በመሆን 70/30 ሁሉን አቀፍ የገጠር ትስስር ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም መሆኑን ጠቁመው የመንገድ ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሲሆን ከ20 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ እንደሚገመት ተናግረዋል።

በወረዳው በ2017 የገባው ፕሮግራሙ በአዲስ መንገድ ግንባታ ፣በመንገድ ጥገና ፣ተንጠልጣይ ድልድይ ፣ስፔሻል እትራከቸር /የድልድይ ስራን እንደሚያከናውን ሀላፊው ገልጸዋል።

መንገድ ግንባታው በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ እንዲጠናቀቅ የአስተባባሪ አካላት ከፍተኛ ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።

በመጨረሻም የደቡብ ጎንደር ዞን አስተዳዳሪ አቶ ጥላሁን ደጀኔ ፣ የደቡብ ጎንደር ዞን የብልጽግና ፖርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ መንበር ክፈተው፣የደቡብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ና የትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደስታ አስራቴ ፣የደቡብ ጎንደር ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ እንድሪያስ ማሩ እንዲሁም የፎገራ ወረዳና ወረታ ከተማ አስተዳደር አመራሮች በተገኙበት የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።

የባጃጅ አሽከርካሪዎች ህግና ደንብ አክብረው ለማህበረሰቡ አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው ተገለፀ። *******በምዕራብ ጎጃም ዞን በፍኖተሰላም ከተማ አስተዳደር ከነዳጅ እጥረት ጋር ተያይዞ የ...
06/05/2026

የባጃጅ አሽከርካሪዎች ህግና ደንብ አክብረው ለማህበረሰቡ አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው ተገለፀ።
*******
በምዕራብ ጎጃም ዞን በፍኖተሰላም ከተማ አስተዳደር ከነዳጅ እጥረት ጋር ተያይዞ የተደረገውን የትራንስፖርት ዋጋ ጭማሪ ለማስተካከል ከባለ ሶስት እግር ባጃጅ አሽከርካሪዎች ጋር ውይይት ተካሄደ።

የምዕራብ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮማንደር ተሾመ ብዙ እንደገለፁት ከመጠላለፍና ከመጠቋቆር ወጥቶ ህግ አክብሮ ሰርቶ የሚለወጥ ተስፋ ያለው ወጣት በከተማው መፈጠር አለበት ብለዋል ።

ከታሪፍ ውጭ ክፍያ የሚስከፈል፣ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ የሚፈጸም እና በተጓዦች ላይ መጉዳት የሚያደርሱ አካላት ላይ የህግ እርምጃ እንደሚወሰድ አሳስበዋል ።

የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አቶ አለልኝ አሰፋ ነዳጅ የሚያቀርቡ ማደያዎች በታሪፉ መሠረት እና በአግባቡ ተደራሽ እንዲያደርጉ እንሰራለን በማለት በማደያዎች ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ አሽከርካሪዎች መረጃ በመስጠት ማገዝ አለባቸው ብለዋል።

የምዕራብ ጎጃም ዞን መንገድ ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ መምሪያ ተወካይ ኃላፊ አቶ ወርቅነህ መንግስቴ አሽከርካሪዎች ህግና ደንብ አክብረው ለማህበረሰቡ አገልግሎት መስጠትና በስነምግባር ደረጃ የተሰጠውን ስልጠና ተግባራዊ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል ።

ተገልጋይ ለመብቱ መታገል እንዳለበት እና ተገቢውን ያገልግሎት ክፍያ መክፈል ግዴታ ነው ሲሉ አቶ ወርቅነህ ተናግረዋል ።

የፍኖተሰላም ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ነብዩ አሽከርካሪዎች በነዳጅ እጥረት ምክንያት ያደረጉትን የዋጋ ጭማሬ በማስተካከል በህግና በመመሪያ መሠረት በተወሰነው ታሪፍ መሠረት ተገቢ ክፍያ እንዲያስከፍሉ ተናግረዋል ።

ከዚህ በተጨማሪም ህግና ደንብ አክብረው ለማህበረሰቡ ፍትሃዊና ተመጣጣኝ አገልግሎት መስጠት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል ።

አሽከርካሪዎች በበኩላቸው የነዳጅ እጥረት ፣ የኑሮ ዉድነት ፣ የመለዋወጫ ዕቃ ዋጋ ጭማሬ በስራቸው ላይ ያመጣውን ተፅዕኖ አንስተው የተደረገው የዋጋ ማስተካከያ እንደገና እንዲታይ ጠይቀዋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ አሽከርካሪዎች ህጋዊ መሆንና ማሟላት የሚገባቸውን ነገር አሟልተው ማሽከርከር እንዳለባቸው መግባባት ላይ በመድረስ ማህበረሰቡም በሚያጋጥሙ ችግሮች ላይ መረጃ በመስጠት ከተቋማት ጋር እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል።

የኤሌክትሪክ ባጃጆች በከተማ የህዝብ ትራንስፖርት ችግር ለመፍታት የተሻለ አማራጭ ሆነዋል።*****ከተማዋ ከፍተኛ የትራንስፖርት ፍላጎትና የትራፊክ መጨናነቅ ያለባት እንዲሁም የሎጂስቲክስ ማዕከ...
03/05/2026

የኤሌክትሪክ ባጃጆች በከተማ የህዝብ ትራንስፖርት ችግር ለመፍታት የተሻለ አማራጭ ሆነዋል።
*****
ከተማዋ ከፍተኛ የትራንስፖርት ፍላጎትና የትራፊክ መጨናነቅ ያለባት እንዲሁም የሎጂስቲክስ ማዕከል በመሆኗ፣ በነዳጅ የሚንቀሳቀሱ ታክሲዎችንና ባጃጆችን በዘመናዊ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የመተካት ስራ በተሻለ ሁኔታ ተከናውኗል።

በዚህም መሠረት፣ በኢትዮ ግሪን የኤሌክትሪክ ባጃጅ ማህበር የተደራጁ ከ7–9 ተሳፋሪዎችን ማስተናገድ የሚችሉ 210 ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ባጃጆች ወደ ስራ በመግባታቸው፣ የህዝብ ትራንስፖርት አቅርቦትን እና የአገልግሎት ጥራትን ፈጣን፣ ቀልጣፋና ምቹ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ ናቸው።

በተጨማሪም፣ እነዚህ አነስተኛ የኤሌክትሪክ ባጃጆች የነዳጅ ፍጆታን በመቀነስ፣ በነዳጅ እጥረት ወቅት አማራጭ በመሆን፣ የአየርና የድምፅ ብክለትን በመቀነስ ለምቹ የትራንስፖርት ስርዓት አስፈላጊ ድጋፍ እየሰጡ ነው።

የኮምቦልቻ ህዝብ ትራንስፖርት መነሻ ከ11 ሺህ ካሬ ሜትር በላይ የሚሸፍን ሲሆን፣ በአንድ ጊዜ እስከ 114 ተሽከርካሪዎችን ማቆምና ማስተናገድ የሚችል ዘመናዊና ደረጃውን የጠበቀ ተቋም ነው።

ምንም እንኳን የአገልግሎት አሰጣጥ በተሻለ ደረጃ ላይ ቢገኝም፣ በቀጣይ የተሻለ ቁጥጥርና ክትትል ለማረጋገጥ የተጀመረውን የኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት በሲሲቲቪ ካሜራዎች መደገፍ ይገባል።

ይህም የታሪፍ ግልፅነትን ለማረጋገጥ፣ የተሳፋሪዎችን ደህንነት ለማሻሻል፣ እንዲሁም የአገልግሎት ጥራትን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለመደገፍ ከፍተኛ ጥቅም አለው።

የኮምቦልቻ ከተማ ትራፊክ ማሳለጫ መንገድ የአስፓልት ንጣፍ ስራ በከፊል፤*****የኮምቦልቻ ከተማ ትራፊክ ማሳለጫ (Bypass) 7.59 ኪ.ሜ የአስፓልት መንገድ ፕሮጀክት በተፋጠነ ሁኔታ እየተ...
03/05/2026

የኮምቦልቻ ከተማ ትራፊክ ማሳለጫ መንገድ የአስፓልት ንጣፍ ስራ በከፊል፤
*****
የኮምቦልቻ ከተማ ትራፊክ ማሳለጫ (Bypass) 7.59 ኪ.ሜ የአስፓልት መንገድ ፕሮጀክት በተፋጠነ ሁኔታ እየተከናወነ ሲሆን ከ45 በመቶ በላይ አፈጻጸም ደርሷል።

ለተሟላ የአስፓልት ማንጠፍ ስራ መሰረት የሆነው 5 ኪ.ሜ የመንገድ ክፍል የሰብ-ቤዝ ስራ ተጠናቆ ወደ አስፓልት ንጣፍ ስራ ተሸጋግሯል። የአስፓልት ንጣፍ ስራው በጥራት ተጀምሮ ቀጥሏል።

በፕሮጀክቱ 5 የተለያዩ አይነትና መጠን ያላቸው ከፍተኛ የኮንክሪት ድልድዮች ግንባታ ስራ ተጠናቋል። ቀሪ 1 ባላ 80 ሜትር ርዝመት ድልድይ በቀድሞው ዋና መንገድ ላይ ለመገንባት የቅድመ ግንባታ ስራዎች በመከናወን ላይ ናቸው።

በከተማ አስተዳደሩ የሶስተኛ ወገንና የግብዓት ማምረቻ ጥያቄዎችን በፍጥነት ከመፍታት ጀምሮ፣ በአሰሪ መስሪያ ቤቱ፣ በስራ ተቋራጩ፣ በአማካሪ ድርጅቶች እንዲሁም በማህበረሰቡ ዘንድ ያለው ትብብር፣ ክትትልና ድጋፍ አበረታች በመሆኑ የፕሮጀክቱ ግብ እንዲሳካ ከነዳጅ አቅርቦትና ትስስር ጋር የተያያዘ ወቅታዊ ችግሮችን በቅንጅት መፍታት ይጠበቃል።

Address

Amhara
Bahir Dar
6000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara RoadTransport and Logistics Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Amhara RoadTransport and Logistics Bureau:

Share