Top international Automotive -ቶፕ ኢትዮ አውቶሞቲቭ

Top international Automotive -ቶፕ ኢትዮ አውቶሞቲቭ Kontaktinformationen, Karte und Wegbeschreibungen, Kontaktformulare, Öffnungszeiten, Dienstleistungen, Bewertungen, Fotos, Videos und Ankündigungen von Top international Automotive -ቶፕ ኢትዮ አውቶሞቲቭ, Geschäft für Autoersatzteile, Berlin.

The best interface for the best mechanics all over the world!follow & Live with us for a better understanding about how to assemble,disassemble,diagnosis,repair and replace of any components of a vehicle ‼መካኒካልና ኤሌክትሪካል ጥገና የሚማሩበት ልዩ ቻናል ቶፕአውቶሞቲቭን ይቀላቀሉ‼

«የጭስ አልባ ከሰል ፈጠራ አሸናፊው ወጣት እዮብ አለሙ እና የ«ብሩህ አዲስ 3» ስኬት»🇪🇹 ግንቦት  9/2018 ዓ.ም 🇪🇹የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣት እዮብ አለሙ በ...
17/05/2026

«የጭስ አልባ ከሰል ፈጠራ አሸናፊው ወጣት እዮብ አለሙ እና የ«ብሩህ አዲስ 3» ስኬት»

🇪🇹 ግንቦት 9/2018 ዓ.ም 🇪🇹

የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣት እዮብ አለሙ በውስጡ የነበረውን የፈጠራ ኃሳብ ወደ ተጨባጭ ሥራ በመቀየር ዛሬ ላይ የብዙዎችን ቀልብ የሳበ ስኬታማ ወጣት ነው።

በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ አዘጋጅነት በተካሄደው «ብሩህ አዲስ 3» የንግድ ሥራ ኃሳብ ፈጠራ ውድድር ላይ ተሳታፊ የነበረው እዮብ አካባቢን የሚጠብቅና ለጤና ተስማሚ የሆነ የፈጠራ ሥራ ይዞ በመቅረብ አሸናፊ መሆን የቻለ ወጣት ነው።

ይህ እዮብ የተሳተፈበት የ"ብሩህ አዲስ" የንግድ ሥራ ኃሳብ ፈጠራ ውድድር በአዲስ አበባ ከተማ በየዘርፉ የሚታዩ ቁልፍ ችግሮችን ለመፍታትና የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር የሚችሉ አዳዲስ ኃሳቦች ይዘው የሚመጡ ወጣቶችን ለማበረታታት የተዘጋጀ መርሃ ግብር ነበር።

የፈጠራ ኃሳቡ መነሻና ማህበራዊ ፋይዳው

ወጣት እዮብ ወደ ጭስ አልባ ከሰል ማምረት ስራ እንዲገባ ያደረገው ዋነኛ ምክንያት። እዮብ በሚኖርበት አካባቢ ሦስት ልጆችን የምታስተዳድርና ቡና በማፍላት የምትተዳደር አንዲት እናት ነበረች። ለዚህች እናት የዕለት ተዕለት ሥራ ትልቅ ወጪና ጫና እየሆነባት የመጣውን የከሰል ወጪ የሚቀንስና ጤናዋን የማይጎዳ አማራጭ ነገር ምን መፍጠር ይቻላል በሚል ጥናት በመጀመር ለዛሬው ስኬቱ መሠረት ጣለ።

ይህ ችግር ፈቺ የፈጠራ አካሄድ የውድድሩን መሠረታዊ ፍልስፍና ሙሉ በሙሉ የሚያንጸባርቅ ነው ምክንያቱም "ብሩህ አዲስ" ወጣቶች ዕውቀትና ክህሎታቸውን መሠረት አድርገው የማህበረሰብንና የተቋማትን ችግሮች የሚፈቱ ሀሳቦችን በማፍለቅ ወደ ንግድ እንዲቀይሩት ማገዝን ዓላማ ያደረገ በመሆኑ ነው ።

የጭስ አልባ ከሰል አሰራር ሂደት

የከሰሉ አሰራር ሂደት ሙሉ በሙሉ የአካባቢን ተረፈ ምርት ጥቅም ላይ የሚያውልና ብክለትን የሚከላከል ነው። እዮብ ግብዓቱን ከተለያዩ የእንጨት ቤቶች የሚወጡ ተረፈ ምርቶችን በመሰብሰብ የካርቦናይዝ የማድረግ ሥራ ይሰራል።

በመቀጠልም ከተዘጋጀው ስታርች ጋር በማደባለቅ፣ በሞልዲንግ ማሽን አማካኝነት የሚፈለገውን ቅርፅ እንዲይዝ ያደርጋል። ይህ ምርት ረጅም ሰዓት የመቆየት አቅም ያለውና በፍጹም ጭስ አልባ በመሆኑ ለቤት ውስጥ አገልግሎት እጅግ ተመራጭ ነው።

እዮብ ስለ "ብሩህ አዲስ 3 የንግድ ሥራ ኃሳብ ፈጠራ ውድድር" መረጃ አግኝቶ በወረዳ ደረጃ ከተመዘገበ በኋላ፣ በክፍለ ከተማው 1ኛ ደረጃን በመያዝ አሸናፊ መሆን ችሏል። ክፍለ ከተማውን በመወከል ወደ ከተማ አስተዳደር ደረጃ የተሸጋገረው እዮብ የ100,000 (አንድ መቶ ሺህ) ብር የገንዘብ ሽልማትና የእውቅና ሰርተፍኬት ተሸላሚ ለመሆን በቅቷል።

በመቀጠልም በፌደራል ደረጃ በደብረዘይት ከተማ በተዘጋጀው የተወዳዳሪዎች የተጠናከረ የስልጠና ካምፕ ላይ ተሳትፏል።

እጅግ በርካታና ጠንካራ የፈጠራ ኃሳቦች በነበሩበት በዚህ ውድድር ላይ እዮብ የፈጠራ ስራውን በሚገባ በማስረዳት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከተመረጡት "ቶፕ 100" ምርጥ አሸናፊዎች ተርታ ውስጥ መግባት ችሏል።

ይህ የእዮብ የውድድር ጉዞ ብሩህ አዲስ የንግድ ኃሳብ ፈጠራ ውድድር ላይ የተቀመጡትን ሦስት የድጋፍ ማዕቀፎች ማለትም ማሰልጠን ፣ መሸለም እና ማብቃት በተግባር ያሳየ ነው ።

ወጣቱ የ"ብሩህ አዲስ 3" ውድድርን በስኬት ካጠናቀቀ በኋላ ኃሳቡን ወደ ሰፊ ንግድ ለመቀየር ትልቅ ጥረት እያደረገ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት የገጠመው ትልቁ ፈተና የማምረቻ ቦታ እጥረት ነው። ፈጠራው በሰፊው ውጤታማ እንዲሆን ሰፊ ቦታ የሚጠይቅ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት የማምረ

Piston ‼ ፒስተን
22/04/2026

Piston ‼ ፒስተን

10/04/2026

በመካኒክነት (አውቶ) ሙያ ኮሌጅ ላይ ስትማሩ ምን ያህል ዕውቀት አገኛችሁ ? እስኪ ከእነምክንያቱ በ% ግለፁት ?

10/04/2026

የሞተር የጀርባ አጥንት ተብሎ የሚጠራው ክፍል የቱ ነው ?
ሀ.ፒስተን ሐ. አልብሮካም
ለ.ኮሎ መ. ቴስታታ

  ‼
10/04/2026

28/03/2026

😍ፊንቴክ
is
ሜይቴክ ።😂

 ?  ?
06/03/2026

? ?

 #የስራ-ቅጥር-ማስታወቂያአዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት በሚከተሉት የስራ ዘርፎች ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ ከታህሳስ 9 ቀን 201...
20/12/2025

#የስራ-ቅጥር-ማስታወቂያ

አዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት በሚከተሉት የስራ ዘርፎች ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ ከታህሳስ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 7 ቀናት ከስር በተጠቀሱት ቅርንጫፎች በአካል እየቀረባችሁ መመዝብ የምትችሉ መሆኑን እገልፃለን።

አዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

 ‼ታህሳስ 10/2018  ዓ.ም በጎንደር ከተማ ጎንደር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ በጥኋቱ ነው የተገኘኹት። በግቢው በርካታ ሰዎች በተለይም ሴቶች የግቢውን ፅዳትና ውበት ለመጠበቅ እየሰሩ አገኘኋቸ...
20/12/2025



ታህሳስ 10/2018 ዓ.ም በጎንደር ከተማ ጎንደር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ በጥኋቱ ነው የተገኘኹት። በግቢው በርካታ ሰዎች በተለይም ሴቶች የግቢውን ፅዳትና ውበት ለመጠበቅ እየሰሩ አገኘኋቸው። በከተማው የሴፍትኔት ፕሮግራም ታቅፈው የእራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ ለመመስረት የሚያስችል ሁለንተናዊ አቅም እየገነቡ የነበሩ ሰልጣኞች ናቸው ለካ ።ያንን ሳይ ቆይቼ ዞር ስል ኮሌጁ በጋርመንት ሙያም በአጫጭር ስልጠና መርሃ ግብር ከአንድ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ተግባር ተኮር ስልጠና የሚያሰለጥናቸው በርካታ ወጣቶችን ተመለከትኩ። ወዳጆቼ ምናልባት በግቢ ውስጥ ሰልጣኞቹ ወይም ሠራተኞቹ ድንገት ቢታመሙ የመጀመሪያ እርዳታ ህክምና ለመሰጠት ዝግጁ የሆነ የክሊንክ ክፍልም ተመለከትኩት።ከዚህ በተጨማሪም ህፃናት ያሏቸው ወላጆች ድንገት ለስልጠና መጠተው ልጆቻቸውን የት እናሳርፍ በለው አይጨነቁም ምክንያቱም የህፃናት ማቆያ ክፍል ተመቻችቶ ይጠብቃቸዋልና። ኮሌጁ የሚገርመው ( DAC) መሠረት አድርጎ ሰልጣኞችን በመደበኛ ፕሮግራም እየተቀበለ ያለ ኮሌጅ ከኮሌጅ በላይ የሆነ ኢንዱስትሪም ነው ቢባልለት ውሽት አይደለም ። በተለይም በእኔ እምነት እና እይታ በአውቶ ሞቲቨ እና በማንፋክቸሪንግ ሙያዎች ጎንደር ፖሊ ተመራጭ የሚያደረጉት እጅ ከአፍ የሚያስጭኑ የተደራጁ ወርክ ሾፖች እና በወርክሾፑ ውስጥ ያሉ የማሰልጠኛ ማሽኖች ናቸው። ስትገቡ ዋው ትላላቹሁ !! የሚገርመው ኮሌጁ አለም አቀፍ ደረጃ በጠበቀ መልኩ የቦሎ እና አፕሮቫል አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። የልዩ ልዩ ማሽን መለዋወጫዎችን መሳሪያዎችንም መስራት የሚችሉ ዘመናዊ የሆኑ በመካኒክስ እና በማሽኒግ የስልጠና ክፍሎች ውስጥ የሰራ ፍስታቹሁን ጠብቀው ተሰድረውለታል። የሚገርመው ኮሌጁ በመደበኛ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ወቅት ተማሪዎች የስልጠና ጥራት ለመቆጣጠር : የተማሪውን ስነመግባር ለማሻሻልና የተቋሙን ደህነንትም ለመጠበቅ ተማሪዎች መማክርት አቋቁሟል። የሰልጠናው ባለቤት ሰልጣኞች ናቸው ማለት ነው አለቀ። ታዲያ እኔም ዛሬ ከጎንደር ከተማ አስተዳደር የሥራ እና ክህሎት መምሪያ እና የኮሌጁ አመራሮች ጋር በአደረኩት ጉብኝት በርካታ ተግባራት ተመለከትኩና ስራቸው ወደ ሌሎች ኮሌጆቻችን እንዲሰፋ በጉብኝቴ ወቅት ያየኋቸውን ምርጥ ተሞክሮዎች : ከ100 ሚሊዮን ብር የኮሪደር ልማት ስራ መሰጠቱ የአካባቢ አመራር አስተዋፅኦ የላቀ ስለመሆኑ:በሀገር አቀፍ ደረጃ 340,000 ዶላር ፕሮጀክት ስለመወዳደሩ : በሰሩት ስራ የፈጠሩት ተጨማሪ ፀጋም ለማድነቅ ፃፍኩት። ታዲያ ኮሌጁ የልዩ ልዩ ማሽኖችን መለዋወጫ ክፍል : የመኪና ሞተሮችን መስራት የሚችል አቅም ያለው ከማሰልጠኛ በላይ ፋብሪካ የሆነ ኮሌጅ ሁኗልና የጎደለውን ሞልተን ወደ ተሟላ ማህበራዊ እና ኢክኖሚያዊ እንቅስቃሴ እናስገባው እላለሁ።

  ‼በኢትዮጵያ በስፋት ስለሚከሰተዉ “የባይቲንግ" የሳይበር ጥቃት አይነት ምን ያክል ያዉቃሉ?በኢትዮጵያ ውስጥ የኢንተርኔት ተጠቃሚ ቁጥር እየጨመረ ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ የባይቲንግ   ጥቃቶች ...
20/12/2025



በኢትዮጵያ በስፋት ስለሚከሰተዉ “የባይቲንግ" የሳይበር ጥቃት አይነት ምን ያክል ያዉቃሉ?

በኢትዮጵያ ውስጥ የኢንተርኔት ተጠቃሚ ቁጥር እየጨመረ ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ የባይቲንግ ጥቃቶች በተለያዩ መንገዶች እየተከሰቱ ይገኛሉ።

ይህ ዓይነቱ ጥቃት በዋነኝነት የሚያተኩረው በሰዎች ጉጉት ወይም ነገሮችን በነጻ የማግኘት ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ነው። በተለይ የሰዎችን የኑሮ ፍላጎት፣ የቴክኖሎጂ እውቀት ማነስ እና በነፃ የሚገኝ ነገር ላይ ያለን ጉጉት ለባይቲንግ ጥቃት በቀላሉ እንድንጋለጥ ያደርገናል።

አጥቂዎችም ይህን ጥቃት ለመሰንዘር ከዚህ በታች የተቀመጡ ሁለት ዋና ዋና የማጥቂያ መንገዶችን ይጠቀማሉ፦

1. በአካል
👉አጥቂው ጎጂ ሶፍትዌር የተጫነበትን USB ፍላሽ ወይም ኤክስተርናል ሃርድ ድራይቭ ሰዎች በሚበዙበት ቦታ (ለምሳሌ፡ ሊፍት ውስጥ፣ ፓርኪንግ ወይም ካፌ) ጥሎ ይሄዳል። ሰውየው "ይህ የማን ይሆን?" በሚል ጉጉት ፍላሹን አንስቶ ኮምፒውተሩ ላይ ሲሰካው፣ ቫይረሱ በራሱ ተጭኖ መረጃ መስረቅ ወይም ኮምፒውተሩን መቆጣጠር ይጀምራል።

2. በኦንላይን
👉በድረ-ገጾች ላይ የሚወጡ አሳሳች ማስታወቂያዎች። ለምሳሌ፦ "እንኳን ደስ አለዎት! የ10,000 ብር ስጦታ ደርሶዎታል፣ እዚህ ይጫኑ" የሚሉ መልእክቶች።

👉ነፃ ፊልም፣ ሙዚቃ ወይም ውድ ሶፍትዌሮችን በነፃ ለማውረድ (Download) ስንሞክር አብረው የሚወርዱ ቫይረሶች አማካኝነት ጥቃቶች ይደርሱብናል።

ከኢትዮጵያ ሳይበር ደህንነት መረጃ

Adresse

Berlin
10115

Benachrichtigungen

Lassen Sie sich von uns eine E-Mail senden und seien Sie der erste der Neuigkeiten und Aktionen von Top international Automotive -ቶፕ ኢትዮ አውቶሞቲቭ erfährt. Ihre E-Mail-Adresse wird nicht für andere Zwecke verwendet und Sie können sich jederzeit abmelden.

Teilen