Mohammed Ousman-መሐመድ ኡስማን

Mohammed Ousman-መሐመድ ኡስማን Am Ethiopian 🇪🇹

 ‼️‼️ከላይ በምስል የምተመለከቱት  ወጣት   ይባላል  በደረሰበት በተሽከርካሪ አደጋ  የእጅ   አጥንት ስብራት   የገጠመው ሲሆን ። ከዚህ ቀደም ህክምና ተደርጎላት የነበረ ቢሆንም መጀመሪ...
28/05/2026

‼️‼️ከላይ በምስል የምተመለከቱት ወጣት ይባላል በደረሰበት በተሽከርካሪ አደጋ የእጅ አጥንት ስብራት የገጠመው ሲሆን ። ከዚህ ቀደም ህክምና ተደርጎላት የነበረ ቢሆንም መጀመሪያ በታሰረበት ሆስፒታል እዛው ተጣሞ ቀርቶ የነበረ ሲሆን በኃላም የተለያየ ቦታ የታከመ ሲሆን ማጠፍ የማይችልበት ሁኔታና የህመም ስሜቱ በርትቶባታል ። ሀክም ክትትል ሲያደርግበት የነበረው ሁስፒታ ወደሌላ ሆስፒታ ሪፈረ የተደረገለት ሲሆን በሽታው ደግም ወደ ነርቭ የተቀየረበት ሲሆን ህክምና አሁን ለይ ካላደረገ እንደሚቆረጥ አዘር ሆሰፒታሉ ነግረውታል ሀኪሞች ታክም መዳን ግን እንሚች የተነገረው ሲሆን ።ለዚህም ከብር 500,000 (አምሰት መቶ ሺ ብር) በላይ እንደሚያስፈልግ ስለተነገረው ። ይህን ለማድረግ ደግሞ ቤተሰብ አቅም የሌለው በመሆኑ ቅን የሆነው የቡታጅራና አካባቢው ህዝብ እንደተለመደው እንዲያግዘን የወጣቱን እጁ ወደነበረበት እንዲመለስ የናንተ ድጋፍ ሲሉ ቤተሰቦቿ ይማፀናሉ።
🙏🙏🙏መልካም ስራ ለነገ ቀን ስንቅ ነው
!! በሚሰቱ የተከፈተ አካውንት 1000390655251 መሰረት መኩሪያ
ሼር በማድርግ ይተባበሩን

የቡታጅራው እንቁ ወጣት  ሚኮ ታሞዋል  😭  ድረሱልኝ እያለን ነው  የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ1ኛ ዓመት ተማሪ የነበረው ወጣት ሙህዲን ተማም (Miko)፣ በድንገት በተከሰተ የኩላሊት መክሸፍና...
22/04/2026

የቡታጅራው እንቁ ወጣት ሚኮ ታሞዋል 😭 ድረሱልኝ እያለን ነው የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ1ኛ ዓመት ተማሪ የነበረው ወጣት ሙህዲን ተማም (Miko)፣ በድንገት በተከሰተ የኩላሊት መክሸፍና የልብ ህመም (የልብ ቫልቭ መስፋት) ህይወቱ አደጋ ላይ ወድቋል። በአሁኑ ወቅት በሳምንት ሁለት ጊዜ የኩላሊት እጥበት (Dialysis) በማድረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ ሙሉ በሙሉ ወደ ጤንነቱ ለመመለስ በህንድ ሀገር የኩላሊት ንቅለ ተከላና የልብ ህክምና ማድረግ ይኖርበታል።

ለዚህ ህክምና ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ስለሚያስፈልገው፣ መላው ኢትዮጵያውያንና በጎ አድራጊዎች በገንዘብ፣ በፀሎትና መረጃውን በማጋራት እንድትተባበሩት ቤተሰቦቹ በአክብሮት ይጠይቃሉ።

ለገንዘብ ድጋፍ (የባንክ ሂሳብ ቁጥር):
• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE): 1000179997251 (ሙህዲን ተማም ከድር)

ለበለጠ መረጃ:
• ሙህዲን (Miko)፦ 0928844406
• ወልዩ ተማም (ወንድም)፦ 0974125709
• ሸህቾ ተማም (ወንድም)፦ 0916688400
• ሸምሰዲን ከድር (አጎት)፦ 0912260701

👉 እባክዎን ይህንን መልዕክት ለሌሎች በማድረስ ለወጣቱ የህይወት ተስፋ እንሁን። የቻላቹትን የአቅማቹ በመርዳችት የበኩላችን እንወጣ

ሼርርር ይደረግ 🙏🙏🙏እባካቹ እርዳታቹን በማድረግ ወንድማችን እናድነዉ ገና  16 አመቱ ነዉ የተጠየቅነዉ 4 ከሚሊየን ብር በላይ ነዉ አቅማችን ስለማይችል የእርዳታ እጃችሁን እንድትዘረጉልን ስ...
26/03/2026

ሼርርር ይደረግ
🙏🙏🙏

እባካቹ እርዳታቹን በማድረግ ወንድማችን እናድነዉ ገና 16 አመቱ ነዉ የተጠየቅነዉ 4 ከሚሊየን ብር በላይ ነዉ አቅማችን ስለማይችል የእርዳታ እጃችሁን እንድትዘረጉልን ስንል በፈጣሪ ስም እንጠይቃለን 🙏...

💔 የቤተሰቡ ጭንቀት እና የሀኪሞች ውሳኔ ​የሀኪሞች ቦርድ ዳዊት ዳግም ጤንነቱ ተመልሶ ወደ ትምህርት ገበታው እንዲመለስ ብቸኛው አማራጭ ወደ ውጭ ሀገር ሄዶ 2 ቱም ኩላሊት ንቅለ ተከላ (Kidney Transplant) ማድረግ እንደሆነ ወስነዋል።

ገና በህፃንነቱ በከፍተኛ ሁኔታ በኩላሊት እየተሰቃየ ይገኛል🥺

ለአንድ ሰው የምታደርጉትን῟ እርዳታ ለሌላው ሙሉ ህይወቱ ነች።"

አካውንት ቁጥሮች🙏

1000 3698 64169 ንግድ ባንክ አክሊሉ ሙሉጌታ

013201746588400 አዋሽ ባንክ አክሊሉ ሙሉጌታ

2956998074211 ዳሽን ባንክ አክሊሉ ሙሉጌታ

199 172 581 አቢሲኒያ አክሊሉ ሙሉጌታ

09 09 85 37 24 ቴሌ ብር አክሊሉ ሙሉጌታ

1000 30 5717 855 ንግድ ባንክ ሙሉጌታ ከበደ

​ለምታደርጉት ማንኛውም ድጋፍ በፈጣሪ ስም ከልብ እናመሰግናለን🙌

የቻልነው ተባብረን ወደ ህክምና እንዲገባ እናድርግ ለወገን ደራሽ ወገን ነው።

05/09/2022

የምስራቅ ጉራጌ ዞን መመስረት እንደ ሀገር ያለው ፋይዳ፣

የምስራቅ ጉራጌ በዞን መመስረት፣ የሀሳብ ብዝሀነት እንዲሰራፋ እና በሀገር ግንባታ ላይ አብሮ ለመሥራት የሚያግዝ ጠቃሚ ሆኖ ሳለ፣ ጎን ለጎን ደግሞ 'ዴሞክራሲያዊ ጠቀሜታው ከፍተኛ ነው።

የምስራቅ ጉራጌ በዞን መዋቅር መመስረት፣ ሰላማዊ እና ፍትሃዊ አሰራርን ወርዶ ተግባራዊ በማድረግ፣ በጋራ የሀገርን ሀብት በጋራ ለማልማት ያስችላል።

እንደ ጉራጌ አውራጃዎች የተለያዩ አመለካከት ሲኖር፣ የሀሳብ ጥራት እንዲገኝ ያስችላል። የምስራቅ ጉራጌ ዞን መመስረት ያስፈልገውም አንድም ለዚህ ነው።

ምስራቅ ጉራጌ ዞን..!!

ግዜው በፈረንጆቹ ኦገስት 1071 አመተ ልደት፣ በቀን 26 በትላንትናዋ እለት ነበር በኢስላም ታሪክ አንዱና ታላቁ የመላዝኪርት ጦርነት የተካሄደው። የሙስሊሞቹ ጦር በአልፕ አርሰላን መሪነት 2...
28/08/2022

ግዜው በፈረንጆቹ ኦገስት 1071 አመተ ልደት፣ በቀን 26 በትላንትናዋ እለት ነበር በኢስላም ታሪክ አንዱና ታላቁ የመላዝኪርት ጦርነት የተካሄደው። የሙስሊሞቹ ጦር በአልፕ አርሰላን መሪነት 20,000 ብቻ የነበረ ሲሆን ሮማን ዲዮጀንስ የሚመራው የመስቀለኞቹ ጦር 200,000 ወታደሮችን አሰልፎ ነበር።

የወታደሮቹን የልብ ትርታ ያዳመጠው ጀግናው አልፕ አርሰላን ታድያ ታይቶ የማይታወቅ ተግባርን ከወነ። ከጦር ልብሱ ስር ከፈኑን በመልበስ "በዚህ ጦርነት ሸሂድ መሆን የፈለገ ብቻ እንደኔ ከፈኑን ለብሶ ይከተለኝ" ሲል አዘዘ። 20,000 ከፈን የለበሰ ጦር አስከትሎም የዲዮጀንስን 200,000 ጦር ገጠመ። በአላህ ፈቃድም ያን ግዙፍ ጦር አንኮታኩቶ ሮማን ዲዮጀንስን መማረክ ችሎ ነበር።

ትላንት የዚህ ታላቅ ጦርነት መታሰቢያ በቱርክ ተከብሯል !!!

ኢትዮጵያ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ጫፍ የረገጠ አስተሳሰብ ያላቸው ሰዎች ሀገር ናት። በታሪክ ጉዳይ ጫፍ ረግጠን አንዱ የአንዱን ታሪክ ለመረዳት ቀርቶ ለመዳመጥ ዝግጁ አይደለም። ሐሳብን እንደግል...
17/08/2022

ኢትዮጵያ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ጫፍ የረገጠ አስተሳሰብ ያላቸው ሰዎች ሀገር ናት።

በታሪክ ጉዳይ ጫፍ ረግጠን አንዱ የአንዱን ታሪክ ለመረዳት ቀርቶ ለመዳመጥ ዝግጁ አይደለም።

ሐሳብን እንደግል ርስት ወስዶ ለማስጠበቅ ከመዉተርተር ይልቅ ሐሳብ የሚቀያየር የሚዋሐድ የሚብሰለሰል ጉዳይ መሆኑን ተረድቶ ሐሳቡን ለማዳበር የሚሞክር ሰዉ ጥቂት ነዉ።

አንዱ የታሪክን እርግማን ሌላዉ የታሪክን ምርቃት ብቻ መስማት የሚፈልግ ከሆነ፣ ልንግባባ አንችልም።

አዲስ ዕዉቀትን የምንሻዉ እና የምንቀበለዉ የቀደመዉ ሐሳባችንን እንዲያጠነክርልን ብቻ ከሆነ ልንለወጥ አንችልም።

ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ

10/08/2022

Don't be upset
One day everything will be OK👌

የህይወት ፅጌረዳዋ የሚፈነዳው ፣ ምንጯ የሚንፎለፎለው በወጣትነትህ ላይ ነው ፡፡ወጣት ከሆንክ የቀጠፍከው የጽጌረዳ እንቡጥ እጅህ ላይ ሊፈካ ይችላል፡፡ወጣት ከሆንክ ልትተክለው ያዘጋጀኸውን የብ...
08/06/2022

የህይወት ፅጌረዳዋ የሚፈነዳው ፣ ምንጯ የሚንፎለፎለው በወጣትነትህ ላይ ነው ፡፡

ወጣት ከሆንክ የቀጠፍከው የጽጌረዳ እንቡጥ እጅህ ላይ ሊፈካ ይችላል፡፡

ወጣት ከሆንክ ልትተክለው ያዘጋጀኸውን የብርቱካን ችግኝ የበሰለ ፍሬ ልትበላ ትችላለህ፡፡

በቃ!!
ወጣት ከሆንክ አለም አይገዛህም ፤ ትገዛዋለህ፡፡ ህይወት አይበይንብህም ፤ ትበይነዋለህ ፤ ዘመን አይቃኝህም ፤ ትቃኘዋለህ፡፡

ታድያ ይህ ሁሉ የሚሆነው የወጣት ልብ ከታደልክ ነው፣ ወጣትነት ግጥምና ዜማ የለውም።

ባለን እምቅ ድንቅ ማንነት ያጨባበጠን ዛሬያችን የትላንት መነሻችን አንዘነጋውም፡፡

የወጣት ልብ ድርና ማጉ ጉጉትና ፍቅር ነው ፤ ጉጉትና ፍቅር ተዋህደው የሚፈጥሩት ብርሃን ነው ወጣትነት፡፡

ወጣትነት በምትጠልቅ ጀምበር ተቅላሎት እንደተዋበ አድማስ ሟች ውበት ሳይሆን ፣ ገና ከአድማስ ማህጸን መውጣት የጀመረች የንጋት ጀምበር የምትነድፈው ብርሃን ነው፡፡

በንጋት ብርሃን አለም ሁልጊዜ አዲስ ናት ፣ ህይወትም እንዲሁ ናት፡፡

ወጣት ከሆንክ ያገጠጠብህ መከራ መሮ ጥርሱ ሳይሆን ፣ ለስላሳው ከንፈሩ ቀድሞ ይታይሀል፡፡ ሊግጥህ ባሰፈሰፈው የመከራ ጥርስ በፍርሃት ለመራመድ ጊዜ የለህም ፤ በከንፈሮቹ ልስላሴ ውበት ተመደህ ፣ ተመስጠህ ትፈላሰፋለህ።

አባትህ ሙሾ ለሚደረድርለት መከራ አንተ ለአዝማሪ ግጥምም ታቀብላለህ።

የልጅነት ጥሪትህን አሟጠህ የነፍስህን መሻት ናኝተህ፣ የህይወትህን ዘፈን ዜማና ግጥም የምትደርሰው አንተው ነህ፡፡

አለም ታጅብሃለች በወጣትነትህ የሙሾ ግጥም ከተቀኘህ አለም የእድር ጡሩንባ አይገዳትም፡፡ በየሰርጉ እርግጫ መንቀል ፤ ምድርን በዱላ ነርታ አዋራ ማጨስ አይከብዳትም፡፡

ለዚህ ደግሞ ከዚህ ከታጨቅንበት ድንኳን የተሻለ መሟገቻ አይገኝም፡፡

📷ጉዞ

Mohammed Ousman

በመለያየትና በበላይነት ጎዳና የተገኘ ትርፍ የለም! FM radio የነበረኝ ቆይታየበላይነትና የመለያየት ጎዳና ተጫጭኖት የቆየው  አለም ይህ  ጉዞ መቋጫው አደገኛ ገደል መሆኑ ግልፅ እየሆነ ...
31/05/2022

በመለያየትና በበላይነት ጎዳና የተገኘ ትርፍ የለም!

FM radio የነበረኝ ቆይታ

የበላይነትና የመለያየት ጎዳና ተጫጭኖት የቆየው አለም ይህ ጉዞ መቋጫው አደገኛ ገደል መሆኑ ግልፅ እየሆነ መጥቷል፡፡

እንኳን የኢትዮጵያውያን የሰው ዘሮች እድል ፈንታ ከመደጋገፍና አንድነት ውጪ አደጋ ውስጥ መውደቁን ፤ከክስተቶቹ መገንዘብ ብልህነት ነው፡፡

ይህ ጎዳና ካደረሳቸው ጉዳቶችና ከጥፋቶች ጭስ እና ከፍርስራሾቹ ስር አዲስ የአንድነትና የአጋርነት መንገድ ብቅ ማለት ጀምሮ ነበር ፡፡ ምንም እንኳን የኋልዮሽ ትንቅንቅ ቢገዳደረውም።

ይህ መንገድ ዳግም አለማችንን እና ህዝቦቿን በዚህች ብርቅዬ ፕላኔት ውስጥ እንደ አንድ የህይወት ቤተሰብ መመልከት የጀመረ መንገድ ነው፡፡

ህልውናችን የተሳሰረ ፤አንዱ በአንዱ ላይ የተመረኮዘ፤ ያልተነጣጠለና የጋራ ፍላጎትና ክብር ፤በመደጋገፍ መስራት አለማችንንና ህዝቦቿን የምንታደግበት መንገድ ነው፡፡

የእንደዚህ ዓይነት አስተሳሰብ ውጤት አጋርነት ነው፤ መጓጓዣው መከባበር ነው፤ መጨረሻው ደግሞ ሰላም ነው፡፡

ይህ እይታ ህይወትን ከነሙሉ የብዝሃነት ሀብቱ ይቀበላል፤ ለእኛም ማለቂያ የሌለው የፈጠራ ዑደት፣ ነጻነትና ተስፋን ይሰጠናል፡፡

የመለያየት መንገድ ደግሞ ልዩነቶቻችንን የተወሰኑ ክፍሎች ከሌላው የተሻሉ፣ የበለጠ ዋጋ ያላቸውና፣ ሁሉ የሚገባቸው ናቸው የሚለውን እምነት ለመደገፍ ይጠቀምባቸዋል፡፡ የዚህ ዓይነት አስተሳሰብ ውጤት የበላይነት ነው፤ መጓጓዣው ጉልበት ነው፤ መጨረሻው ደግሞ ጥፋት ነው፡፡ ይህ እይታ ህይወትን ያቀጭጫል፣ እኛንም በማያቋርጥ የጸብ፣ የጭቆናና የትግል ዑደት ውስጥ ይከተናል፡፡

ይህ እንግዲህ እያንዳንዳችን በየራሳችን ህይወት ውስጥና ህይወታችንን በምንመራበት አኳኋን ላይ ልንመርጠው የሚገባ ምርጫ ነው፡፡ የአንድነትንና የአጋርነትን መንገድ የምንመርጥ ሰዎች የአዲስ ነገ ጀማሪዎች ነን፡፡ አሮጌው ዓለም በዙሪያችን በሚፈራርስበት ጊዜ አዲስ ዓለም እየገነባን ነው ማለት ነው... ወዘተረፈ።

B t a j I r a E t h I o p I a

ቡታጅራ ከተማ በፎቶ📷
30/05/2022

ቡታጅራ ከተማ በፎቶ📷

Address

Butajira

Telephone

+251928832072

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mohammed Ousman-መሐመድ ኡስማን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share